የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ሠራተኞችና አመራሮች ተ...

image description
- In ንግደረ    0

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ሠራተኞችና አመራሮች ተስፋን እንትከል በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካሄዱ።

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ሠራተኞችና አመራሮች ተስፋን እንትከል በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አካሄዱ።

ሰኔ 23/2018 ዓ ም

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ተስፋን እንትከል በሚል መሪ ቃል በቦሌ ክ/ከተማ ቡልቡላ አካባቢ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሂዷል።

በችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩ በመገኘት አረንጓዴ አሻራቸውን ያኖሩት የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሀቢባ ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ የምንተክለው ችግኞችን ብቻ ሳይሆን የነገ ተስፋችንን ጭምር ነው ብለዋል።

እንደ ወ/ሮ ሀቢባ ገለፃ ባለፉት 8 አመታት በክቡር ጠቅላይ ሚንስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት ባለፉት ስምንት አመታት በተካሄደ ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ዘመቻ እንደ አገር 48 ቢልዮን የሚሆኑ ችግኞችን በመትከል 2.8% የነበረውን አጠቃላይ የደን ሽፋን 24% ማድረስ መቻሉን አሳውቀዋል።

በመጨረሻም ችግኞችን መትከል ብቻ ሳይሆን በየጊዜው እየተንከባከቡ ማፅደቅ ከሠራተኛውና ከአመራሩ ይጠበቃል በማለት መልዕክት አስተላልፏል


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments